ተፈላጊው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ዋለ

Tuesday, 02 October 2018 06:17

*********************************
መስከረም 01 ቀን 2011 ዓ/ም በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ሲሆን በቂርቆስ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው ቦልጋሪያ ( የድሮ በግ ተራ ) ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕድሜያቸው የ19 እና የ20 ዓመት የሆኑ እህትማማቾችን የመኪና አደጋ በማድረስ የተሰወረው የፖሊስ መኪና አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል፤ ምርመራውን በማጣራት ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ሲሆን ተከሳሹ አደጋውን ካደረሰ በኋላ ላለፉት 19 ቀናት ተሰውሮበት ከነበረው ከምስራቅ ጎጃም ደንባ ወረዳ በክትትል መያዙ ታውቋል፡፡ 
ተጠርጣሪውን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ አድካሚ ፍለጋ ማድረጉንም ተገልጧል፡፡ ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ከሚጻፉት ጉዳዮች ይልቅ፤ ወደ ኮሚሽኑ በመምጣት መረጃ ማግኘት የሚችል መሆኑ ተገልፀዋል፡፡

Rate this item
(1 Vote)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus