ዕውቅናና ማበረታቻ ተሰጠ!

Friday, 05 October 2018 14:28

ዕውቅናና ማበረታቻ ተሰጠ!

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በስራ እንቅስቃሴዎቻቸው ጎልተው በመውጣት ከተጠርጣሪዎች የገንዘብ መደለያ አንቀበልም ሲሉ ለህግ በማቅረብ ለሰሩት አኩሪ ተግባር ለአመራርና ለአባላቱ የገንዘብ ሽልማት ሰጥቷል፡፡ መስከረም 12 እና መስከረም 22 ቀን 2011 ዓ/ም በተዘጋጀው የእውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ላይ የተገኙት ኮሚሽነር ደግፌ በዲ የከተማዋን ነዋሪዎች የፍትህ ጥያቄ በአግባቡ ሊመልስ የሚችል የፖሊስ ኃይል ለመፍጠር ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረው ለተሸላሚዎቹ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ም/ኮሚሽር ዘላለም መንግስቴ በበኩላቸው መንግስት የጥቁር ገበያን ለመግታት በጀመረው ዘመቻ የኮሚሽኑ አባላት ከሁለት ሚሊየን እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር ድረስ ከተጠርጣሪዎች የቀረበላቸው መደለያ ሳያጓጓቸው ተጠርጣሪዎችን ለህግ በማቅረባቸው የፖሊስ ተቋሙን ያኩሩ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም መሰል ማበረታቻዎች እንደሚቀጥሉ ገልፀው አዳዲስ የፖሊስ አባላትም ከዚህ አርአያነት ካለው ተግባር ብዙ ትምህርት ሊማሩ ይገባል ብለዋል፡፡
የፖሊስ ስራ በትልቅ መስዋዕትነት ውስጥ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ም/ኮሚሽነር ሀሰን ነጋሽ ይህ ማበረታቻ ሙያዊ ስነ ምግባራቸውን ጠብቀው ለሚሰሩ አባላትና አመራሮች ትልቅ ብርታት ነው ብለዋል፡፡
በዝግጅቱ ላይ የ20ኛ ዙር የፖሊስ አባላት አቀባበል የተደረገ ሲሆን የፖሊስ አመራሩና አባላቱ ላከነወኑት ተግባር አድናቆታቸውን ገልፀው አርአያነታቸውን እንደሚከተሉም ተናግረዋል፡፡
com.shilmatcom2 shilmatshilmat 2

Last modified on Friday, 30 November 2018 06:58
Rate this item
(2 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus