ፖሊስ ዜና

ሃገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሃገር ቤት የመጡ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች አዲስ አበባ ፍፁም ሰላም የሰፈነባት ከተማ መሆኗን ማረጋገጣቸውን ተናገሩ፡፡በመላው ሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
*******
ኢትዮጵያ ተጣርታ አልቀርም በማለት ኑሯቸውን በተለያዩ ሃገራት ያደረጉ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ ሃገር ቤት በመግባት ላይ ናቸው፡፡
የዲያስፖራው ማህበረሰብ በቃ ወይም # NO MORE በሚል ጠንካራና ተከታታይ ሰልፍ በማድረግ የኢትዮጵያ ልሳን በመሆን የሀገራቸውን ድምፅ ሲያሰሙ መቆየታቸው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር ሊቀመንበር አቶ እንድሪስ መሃመድ በተለይ ለአዲስ ፖሊስ ገልፀዋል፡፡ ማህበራቸው ልዩ ልዩ ሃገራዊ ጉዳዮችን በማስተባበር በውጪ የሚገኙ ዜጎች ለሃገራቸው እድገት እና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በአውሮፓ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አስተባባሪ አቶ ሰለሞን አሻግሬ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት ሃገራችንን ያጋጠማትን ችግር ለመቅረፍ መላው ህዝብ እየተረባረበ እንደሆነና የዲያስፖራው ማህበረሰብም የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን በማስታወስ አሁን የተጀመረው የሃገርን ጥቅም የማስጠበቅ እንቅስቃሴን አጠናክረን በመቀጠል የሃገራችንን ችግር በዘላቂነት ልንፈታ ይገባል ብለዋል፡፡
ነዋሪነታቸው በአሜሪካ ሚኒሶታ የሆነው ወ/ሮ ዘኒ ተሾመ ሃገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት እንደመጡና እየተደረገ ባለው አቀባበል በጣም መደሰታቸውን አስረድተው ያለው የፀጥታ ሁኔታ አስተማማኝ በመሆኑ የገና በዓልን ለማክበር ወደ ላሊበላ ለመሄድ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ወደ ኢትዮጵያ የመምጣታቸው ዋነኛ ምክንያት ስለ ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያ ተቋማት የሚነገረውን የተዛባ መረጃ ሃሰት መሆኑን ለመላው ዓለም ለማሳወቅና ለሃገራቸው እና ለወገናቸው ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት እንደሆነ ከአዲስ ፖሊስ ጋር ቆይታ ባደረጉበት ወቅት ሃሳባቸውን አጋርተውን ይህን በማድረጋቸውም ሀገራዊ ኩራት እንደተሰማቸው እንግዶቹ ገልፀዋል፡፡
የዲያስፖራ አባላቱ በተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው ከተማችን አዲስ አበባ ፍፁም ሰላም የሰፈነባት እንደሆነች በተለያዩ ስፍራዎች ተዘዋውረው ማረጋገጣቸው አስታውቀው በመላው ሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡1111

መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም ኢትዮጵያ በአዲስ መንግስት ፣በአዲስ ተስፋ አዲስ ምዕራፍ የምትጀምርበት ቀን ነው ፡፡
የጋራ ግብረሀይሉ ከፌዴራል ፖሊስ፤ከብሔራዊ መረጃ ደህንነት፤ከመከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር አስቀድሞ ዕቅድ በማውጣት እና ህብረተሰቡን በማሰተባበር የተከናወኑት ተግባራት ውጤት አስገኝተዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተከናወነው የአዲስ ምዕራፍ በዓለ-ሲመት በሰላም መጠናቀቁን የፀጥታ የጋራ ግብረሀይሉ አስታውቋል፡፡
ሥነ-ሥርዓቱ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅም በፍፁም ሙያዊ ብቃት ኃላፊነታቸውን ለተወጡ ለመላው የፀጥታ አካላትና ለሰላም ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች የፀጥታ የጋራ ግብረ-ሀይል ከፍ ያለ ምስጋናውን በታላቅ አክብሮት ያቀርባል፡፡
ለዜጎች ሰላም መረጋገጥ እንዲሁም የቁልፍ መሰረት ልማቶችን ደህንነት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመጠበቅና ስጋቶችን ለመከላከል ሲባል ድሮኖችን ያለምንም ህጋዊ ፈቃድ ለቀረፃ መጠቀምም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡
የሀገሪቱን ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም የመጠበቅ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑን የጠቀሰው ተቋሙ አንዳንድ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሚመለከተው አካል ህጋዊ ፈቃድ ሳያገኙ ድሮኖችን በሀገሪቱ በሚካሄዱ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ህዝባዊ ሁነቶች ላይ ለቀረፃ ሲጠቀሙ እና ሲያበሩ እየተስተዋለ መሆኑን ገልጿል፡፡
እነዚህ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጉዳዩ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አውቀው ከህገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አሳስቧል፡፡
ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ ድሮኖችን ለቀረፃ ሲጠቀም እና ሲያበር የተገኘ ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ በህግ እንደሚጠየቅ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስጠንቅቋል።
መረጃውን ያገኘነው ከኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ ነው
ምናልባት የ'መረጃና ደህንነት የብሔራዊ ETHIOPIA እልግባል አገልግሎት NISS NATIONAL AND SECURITY INTELLIGENCE SERVICE' የሚል ጽሑፍ ምስል
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ሚካኤል አደባባይ አካባቢ መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ም/ኢ/ር ጃፋር አሊ እና ኮንስታብል መስፍን በተለ የተባሉ የቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አባላት አንዲትን ግለሰብ በአስነዋሪ ሁኔታ በመደብደባቸው በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጠራ ይገኛል፡፡
ህዝብን በሰብአዊነት ማገልገል የአዲስ አበባ ፖሊስ መርህ መሆኑ እየታወቀ ነገር ግን አንዳንድ አመራሮችና አባላት ይህን መርህ በመተላለፍ የሚፈፅሙት ህገ-ወጥ ድርጊት ተቋሙ የማይታገስ መሆኑን ገልፆ በ2013 የበጀት ዓመት ብቻ እንኳን በልዩ ልዩ ጥፋት ላይ የተገኙ 171 የፖሊስ አመራሮችና አባላት ከሰራዊቱ እንዲሰናበቱ አድርጓል፡፡
ከስራ ከተሰናበቱት 29ኙ ከሰብአዊ መብት ጥስት ጋር በተያያዘ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል። ህግን በመተላለፍ ጥፋት በሚፈፁም አባላት እና አመራሮች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፖሊስ አስታውቆ ህብረተሰቡ እንዲህ ዓይነት ከፓሊስ የሙያ ስነ- ምግባር ውጪ የሆኑ ድርጊቶች በሚፈፀሙበት ወቅት በፍጥነት ጥቆማ እንዲያደርግ እየገለፅን ግለሰቧን በደበደቡ የፖሊስ አባላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዶ ውጤቱን ለህዝብ የሚሳውቅ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ለመታደም በርካታ እንግዶች ወደ አዲስ አበባ ስለሚመጡ እንግዶች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳይ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ህብረተሰቡ በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ መልዕክት ተላፏል፡፡
በሀገራችን የተካሄደውን 6ኛውን ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተወሰኑ ክልሎች መንግስት መመስረታቸው ይታወቃል፡፡
የተለያዩ ሀገራት ፕሬዝዳንቶች ፣ ጠቅላይ ሚኒስተሮች ፣ የሀገራት ተወካዮች እንዲሁም የክልል ፕሬዝዳንቶች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች በሚገኙበት መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም የኢፌዲሪ መንግስት ይመሰረታል፡፡
የመንግስት ምስረታው በስኬት እንዲጠናቅ እንዲሁም የኢሬቻ እና የመስቀል በአላት በሰላም እንዲከበሩ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡
ግብረ ኃይሉ እቅድ በማውጣት እና ህዝብን በማሳተፍ ባከናወናቸው ተግባራት በዓላቱ በሰላም ተከብረዋል፡፡
ህብረተሰቡ በቅረቡ የተከበሩት የኢሬቻ እና የመስቀል በዓላት በሰላም እንዲከበሩ እንዲሁም በአጠቃላይ ለፀጥታው ስራ ስኬታማት እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ የሚበረታታ ነው፡፡
በአላቱ በሰላም እንዲከበሩ ህዝቡ እንደሁል ጊዜው ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም ላደረገው ቀና ትብብር እንዲሁም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ኃላፊናታቸው በብቃት ለተውጡ የፀጥታ አካላት አመራሮችና አባላት የጋራ ግብረ ኃይሉ ምስጋናውን እያቀረበ የመንግስት መስረታው ፕሮግራሙ በውጤት እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን ያስተላፋል፡፡
የፕሮግራሙ ታዳሚዎች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳዮች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ግብረ ኃይሉ ጥሪውን እያቀረበ የመንግስት ምስረታው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፡-
1. ከሚያዚያ 27 አደባባይ ወደ ውጪ ጉዳይ ሚ/ር
2. ከአዋሬ በአዋሬ ገበያ ወደ ፓርላማ
3. ከሴቶች አደባባይ ወደ ካሳንቺስ
4. ከሴቶች አደባባይ በእንድራሴ ሆቴል ወደ ካሳንቺስ ቶታል
5. ከ22 ወደ ቅዱስ ኡራኤል እንዲሁም ከኤድናሞል በአትላስ ሆቴል ወደ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን
6. ከአትላስ ሆቴል በደሳለኝ ሆቴል ሩዋንዳ
7. ከኤምፔሪያል ሆቴል ወደ ብራስ ሆስፒታል
8. ከገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ውስጥ ውስጡን ወደ ብራስ ሆስፒታል
9. ከጎሮ አዲሱ መንገድ መሄጃ ወደ ብራስ ሆስፒታል
10. ከቦሌ ሚካኤል ወደ ቀለበት መንገድ እንዲሁም ከቦሌ ሚካኤል ወደ ሩዋንዳ ማዞሪያ
11. ከካዲስኮ አደባባይ ወደ ቦሌ ሚካኤል ዋናው ቀለበት መንገድ
12. ከቡልቡላ ወደ ቦሌ ሚካኤል
13. ከመስቀል ፍላውር ወደ ጎርጎሪዮስ አደባባይ
14. ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር አጎና ሲኒማ
15. ከጎፋ ማዛሪያ አዲሱ መንገድ መስቀለኛ ወደ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያ ለገሃር
16. ከቡልጋርያ ማዞሪያ ወደ ገንት ሆቴል እንዲሁም ከቡልጋርያ ማዞሪያ ወደ አፍሪካ ህብረት አደባባይ
17. ከልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር እንዲሁም ከከፍተኛ ፍርድ ቤት ኑር ህንፃ በባልቻ መስቀለኛ ወደ አረቄ ፋብሪካ
18. ከ18 ወደ ጦር ሃይሎች 3 ቁጥር ማዞሪያ የሚወስደው ከላይም ከታችም
19. ከሞላ ማሩ ወደ ቅድስት ልደታ ቤተ-ክርስቲያን
20. ከተክለ ሃይማኖት በርበሬ በረንዳ ወደ ዲ-አፍሪክ ሆቴል
21. ከተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል
22. ከአብነት ፈረሳኛ በቀድሞ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቴአትር
23. ወሎ ሰፈር፣ ኦሎምፒያ፣ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ- መንግስት ግቢ ገብርኤል መታጠፊያ ሸራተን አዲስ አራት ኪሎ
24. ጎርጎሪዮስ አደባባይ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም ፕሮግራሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቅ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ለትራፊክ ዝግ ሲሆኑ ፕሮግራሙ በሚካሄድበት መስቀል አደባባይ አካባቢ ከዛሬ መስከረም 23 ቀን 2014 ዓ/ ጀምሮ በሁለቱም አቅጣጫዎች ግራና ቀኝ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሸከርካሪን አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የፀጥታና ደህንነት ግብረኃይል አስታውቋል፡፡
እንግዶች በአጀብ ሆነ ለልዩ ልዩ ጉዳይ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ህብረተሰቡ በተለይ ደግሞ አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ግብረ ኃይሉ መልዕክቱ አስተላልፏ ።
ፎቶው ዝርዝር መግለጫ የለዉም
 

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለመላው አመራሮችና አባላት በሦስት ዙር የሠጠውን የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡ ወቅቱ የሚጠይቀውን ፖሊሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ተቋሙን በቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ጣሰው ገልፀዋል፡፡3
በኮሚሽኑ ከመጋቢት 9 እስከ ሚያዚያ 9 ቀን 2011 ዓ/ም በሦስት ዙር ለመላው አመራሮችና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ሚያዚያ 10 ቀን 2011 ዓ/ም በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ጣሰው ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የፀጥታ አካላትን ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 2
ኮሚሽነር ጀነራሉ አያይዘው ሀገራችን በለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝድ እና ለውጡ ህዝባዊና ህገ-መንግስታዊ መሆኑን በመጥቀስ በህዝብ ፍላጎት የመጣው ለውጥ የታለመለትን ግብ እንዲመታ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ ሚና አላቸው ብለዋል፡፡3
ለውጡ በፖሊስ ተቋማት ውስጥ ስኬታማ እንዲሆን እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ፖሊሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ተቋሙን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን የጠቁሙት ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ጣሰው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከምንም በላይ ለሰው ሀብት ልማት እና ለኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የፖሊስ አመራሮችና አባላት የለውጡን ባህሪ ተገንዝበው በተለይ ሰብዊ መብቶችን አክብረው በማስከበር ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በበኩላቸው ህዝብና መንግስት ቅን አገልጋይ እንደሚፈልጉ ተናግረው ኮሚሽኑ የለውጡ አካል በመሆን ህዝባዊና ዲሞክራሲያዊ የፖሊስ ተቋም በመገንባት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገችና እየዘመነች ለምትገኘው ከተማችን የሚመጥን የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ 54
ስልጠናው የአመራሮችን እና የአባላትን የማስፈፀም አቅም ለማጎልበት የራሱ ጠቀሜታ ማበርከቱን ኮሚሽነር ጌቱ በንግግራቸው ጠቁመው መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡
በስልጠናው ማጠቃለያ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በቅርበት ከሚሰሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎ ሺፕ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፓስተር ዳንኤል ገ/ስላሴ ልዩ ልዩ መልክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን ተቋማቸው ለፀጥታ አካላት የሚሰጠውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡በአስራ ሦስት የተለያዩ ስፍራዎች በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተደግፎ በተሰጠው ስልጠና ላይ የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ስልጠናውን ተከታትለውታል፡፡

       የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም ፤ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና የሌሎች አስፈፃሚ አካላትን የ2011 በጀት ዓመት በ9 ወር የተከናወኑ የፀጥታማስከበርስራዎችን በጋራ ገምግመዋል፡፡በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡11

     በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሚያዚያ 10 ቀን 2011 ዓ.ም የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የተከበሩ አቶ ኤፍሬም ግዛው የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም ፡ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፤ እና ሌሎች የም/ቤቱ አባላት፤የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ፤ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፤የሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና ከደንብ ማስከበር ዘርፍ የተውጣጡ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡  22

  

     የአዲስ አበባ ፖሊሰ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በመዲናችን ወንጀልን እና የትራፊክ አደጋን   ለመቀነስ እንዲሁም የተጀመረውን ሃገራዊ ለውጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የኮሚሽኑ አባላትና አመራር ልዩ ትኩረት ሰጥተው ለህብረተሰቡ ስጋት የሆኑ ወንጀሎችን ለመቀነስእየሰሩ መሆኑን ገልፀው ፡ ከሪፖርቱ የተገኙ መልካም አፈፃፀሞችን በማጠናከርና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በቀጣይ ከከተማው ማህበረሰብ፤ከአስፈፀሚና ከአስተዳደር አካለትጋር በመቀናጀት እንደሚሰሩ በመጠቆም የህ/ቡ እና የተቋማት ድጋፍና አጋርነት ወሳኝ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡ 33 

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም፤ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ኤፍሬም ግዛው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተማውን ሁለንተናዊ ሰላም በማስፈን በርካታ የሚታዩና የሚለኩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡በቀጣይ በጋራ በመተባበር የተጀመረውን ለውጥ እንዳይደናቀፍ ማስቀጠል፤የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት፤የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እና ሌሎች መልካም ተግባራት በተቀናጀ መልኩ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችም በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡      

በዕለቱ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የዕቅድና በጀት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ማሞ የአስፈፃሚ ተቋማት በጋራ ለመስራት ያቀዱትን የህዝብ ስራ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ እና ያለ ህዝብ ትስስር የሚሰራ ስራ ውጤቱ አርኪ ስለማይሆን ከምንም በላይ የህ/ቡ ተሳትፎ ማደግ አለበት ብለዋል፡፡44

ለጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ እና ግምቱ ከ1ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ከህብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መያዙን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

1Capture 6በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው በተለምዶ 7ኛ ሸንኮራ በረንዳ ተብሎ ከሚጠራ አካባቢ ከሚገኘው «ትዕግስት ብሩክ ቶታል ማደያ»ውስጥ ጥር 12 ቀን 2011 ዓ/ም የተቋሙ ሰራተኞች ከህገ-ወጦች ጋር በመተባበር በ44 ጀሪካን 995 ሊትር ቤንዚን ከማደያው በመቅዳት ላይ እንዳሉ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት የተቀዳውን ቤንዚን እና ሌላ ሊቀዳበት የነበረ 44 ባዶ ጀሪካን እንዲሁም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 አ/አ 29642 አይሱዙ ተሽከርካሪን ከአምስት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዚዮን ኃላፊ ኮማንደር ጌታነህ በቀለ ገልፃዋል፡፡

የማደያው ሰራተኞች ቤንዚን በጥቁር ገበያ ከሚሸጡ ህገ-ወጦች ጋር በመተባበር ድርጊቱን መፈፀማቸውን ፖሊስ በምርመራው ማረጋገጡን ፤ በህገ-ወጥ ተግባሩ ላይ ተሳትፎ ያደረጉ አምስት ግለሰቦች ምርመራ እየተጠራባቸው እንደሚገኝ ኮማንደር ጌታነህ አስረድተዋል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋለው ቤንዚን ከ11 ሺ ብር በላይ ዋጋ እንደሚያወጣ ኃላፊው ተናግረው በልዩ ልዩ ጊዜያት ግምቱ 38 ሺ ብር በላይ የሚያወጣ 112 ጀሪካን ቤንዚን ተይዞ ምርመራው ተጣርቶ የምርመራ መዝገቡ ለዓቃቤ ህግ መላኩን ከኮማንደሩ ገለፃ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም ታህሳስ 8 ቀን 2011 ዓ/ም ልዩ ቦታው አማኑኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ ኮድ 3-47453 አ/አ የሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ከላይ ሲሚንቶ በማድረግ ከስር 63 ጀሪካን ቤንዚን ጭኖ ሲንቀሳቀስ በድንገተኛ ፍተሻ መያዙን ኮማንደሩ አስረድተዋል፡፡  

በተያያዘ ዜና ጥር 13 ቀን 2011 ዓ/ም ምዕራብ ሆቴል አከባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 80502 አ/አ የሆነ ተሽከርካሪ ግምቱ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ በኮንትሮ ባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ልዩ ልዩ እቃዎች ይዞ ሲንቀሳቀስ ፖሊስ መምሪያው ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተሽከርካሪውን መያዙን ነገር ግን አሽከርካሪውን ለመያዝ ክትትል እየተደረገ መሆንን ኮማንደር ጌታነህ ገልፃዋል፡፡Capture 8

ተሽከርካሪው በብርቱ ክትትል ሲያዝ በርከታ ጣቃ ጨርቆች ፣ 2ሺ የሞባይል ቻርጀሮች ፣ 3480 አይነቱ «ኑር ሴላ»የሆነ ሲጋራ እና 1ሺ የሪሲቨር ሪሞት ኮንትሮል ይዞ ለማለጥ ሲሞክር እንደተያዘ ሀላፊው አስረድተዋል፡፡

መርካቶ የንግድ ስፍራ በመሆኑ በተለይ የኮንትሮ ባንድ ንግድ እንደሚስተዋል እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቤንዚን በጥቁር ገበያ ለመሸጥ እንቅስቃሴ መኖሩን ነገር ግን ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሚሰጠው ጥቆማ አብዛኞቹ እየተያዙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ህገ-ወጥነትን በጋራ መከላከል የሚቻለው ህዝብና ፖሊስ በጋራ ሲጣመሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልፆ ህዝቡ ጥቆማ በመስጠትና አጥፊዎች በህግ እንዲጠየቁ ምስክር በመሆን እያረገ ያለውን የነቃ ተሳትፎ አጠናከሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ኮሚሽኑ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡Capture 2Capture 16 - CopyCapture 4Capture 13

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ በልዩ ልዩ ሙያ ያሰለጠናቸውን የፖሊስ አመራሮች አስመረቀ፡፡ ከተመራቂዎቹ 57ቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ናቸው፡፡ በምረቃው ላይ የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየተደረገ ባለው ጥረት ፖሊስ ኃላፊነቱን በብቃት ሊወጣ እንደሚገባ መልእክት ተላፏል፡፡EPUC
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ ታህሳስ 27 ቀን 2011 ዓ/ም በፖሊስ ሳይንስ ፣ በወንጀል መከላከል፣ በወንጀል ምርመራ ፣ በፖሊስ ማናጅመንት እና በጤና የትምህርት ዘርፎች በድግሪ እንደዚሁም በወንጀል ምረመራ ዲፕሎም እና በጤና ደረጃ 2 በአጠቃለይ 481 አመራሮችን አስመርቋል፡፡ 
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፣ ክብርት ሙፈሪያት ካሚል የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ፣ ክቡር አቶ እንደሻው ጣሳው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል እና ሌሎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የፖሊስ አመራሮች በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዋል፡፡EPUC1
የተረጋጋ ኢኮኖሚ እና ፖሊቲካ ሂደት ለማስፈን በጥቅሉ የሰከነ ተውልድ ለመገንባታ በእውቀት ፣ በክህሎት እና በአመላካከለቱ የጠነከረ የፖሊስ አመራርና ባለሙያ ማፍራት እንደሚያስፈልግ ክብርት ፕሬዝዳንቷ ባደረጉት ንግግር ገልፀው ፖሊሶች ተልዕኳቸውን ለመወጣት ቁርጠኛ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል፡አንድ ፖሊስ በተላበሰው መልካም ስብእና እንደሚለካ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አስታውሰው ፖሊሶች ከራስ ይልቅ ለህብረተሰብ ጥቅም ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ተመራቂዎችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ 
የፖሊስ ዮኒቨርስቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጀኔራል ቀናዓ ያደታ በበኩላቸው ኮሌጁ ከተቋቋመበት 72 ዓመታትን ያስቆጠረ አንጋፋ የትምህርት ተቋም መሆኑን አስታውሰው በእነዚህ ዓመታት ዩንቨርስቲ ኮሌጁ በርካታ የፖሊስ አመራሮችን ማፍራቱን ተናግረው ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በአደረጃጀት ፣ በአሰራር ፣ በሰው ኃይል እና በቴክኖሎጂ ራሱን ለማደረጃት እንዲሁም የመምህራንን የማስተማር ዘዴ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ማለቂያ እንደሌለው የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ገልፀው ተመራቂዎች ከኮሌጁ ያገኙትን እውቀት በተግባር ከሚያገኙት ልምድ ጋር በማጣመር ህዝባዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በቆይታቸው ወቅት በርከታ እውቀቶችን መገበየታቸውን ያነጋገርናቸው ተመራቂ አመራሮች ተናግረው በአሁኑ ወቅት ሀገራችን የጀመረችውን ለውጥ ስኬታማ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡EPUC3
ከአጠቃላይ ተመራቂዎች መካከል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፡-
• በጀረኒክ የመጀመሪያ ድግሪ -25
• በመደበኛ ዲፕሎማ 41ኛ ዙር -12
• በወንጀል ምርመራ ዲፕሎማ- 10
• በድህረ ምረቃ ዲፕሎማ 8ኛ ዙር -4
• በስፔሻል ድግሪ 6 በድምሩ 57 አመራሮችን አስመርቋል፡፡ ለተመራቂ አመራሮች የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የእንኳን ደስያላችሁ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡EPUC4EPUC8

አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከጀስቲስ ፎር ኦል-ፒኤፍ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብት ዙሪያ በአዳማ ከተማ ለኮሚሽኑ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስለጠና ሠጠ፡፡ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ

ታህሳስ 11 እስከ 13 ቀን 2011 ዓ.ም   በአዳማ ከተማ በተሰጠው ስልጠና ላይ ተገኝተው የስራ መመሪያ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እንደገለፁት በሀገራችንም ሆነ በተቋማችን የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ለመስቀጠል ማህበረስቡ በየደረጃው የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በፍጥነት ከመመለስ አንፃር ሳይንሳዊ በሆነ የአመራር ክህሎት በመታገዝ ሰዎች በተፈጥሮ ያገኙትን ሰብአዊ መብታቸውን በማንኛውም ሁኔታ እንዲከበር ለማድረግ ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው ለለውጡ መሳካት የአመራርንት ሚናቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ ኮሚሽኑ ከመቼውም ጊዜ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን ም/ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡km mekonen

የኮሚሽኑ ፖሊስ አካዳሚ ዳይሬክተር ረ/ኮሚሽነር መኮንን አሻግሬ በበኩላቸው የፖሊስ ተቋም አመራሮችና አባለት ሰብአዊ መብትን አክብሮ የማስከበር ድርብ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስታውሰው በተወሰ መልኩ በፀጥታ ኃይሉ የሚስተዋሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል ስልጠናው ለአመራሩ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር ስለታመበት መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡

የፖሊስ አመራር ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ በቅድሚያ ጥሰቶቹን አስቀድሞ መከላከል ይገባል፡፡ ጥሰቶች ተፈፅመው ሲገኙ በፍጥነት ለህግ በማቅረብ ረገድ ፖሊስ ህገ መንግስቱንና በስሩያሉትን ህጎች መሰረት አድርጎ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ መጠን ሰባአዊ መብቶችን አስቀድሞ ከማስከበር በተጨማሪ የማስከበር ግዴታውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ስልጠናውን የሰጡት ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ ገልፀዋል ፡፡Docter  sisay

ለአመራሮቹ ስልታዊ የአመራር ዘዴዎች በተመለከተ እንደተቋም የለውጥ ግለቱን ለማስቀጠል አመራሩ ዘመኑ የሚጠይቀውን ሳይንሳዊ የአመራር ጥበብን በመጠቀም ቀልጣፋና ተደራሽ በየትኛውም ሁኔታ ለህግ የበላይነት ተገዥ የሆነ ቨመራር መኖር እንዳለበት ረ/ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ተሾመ ገልፀዋል፡፡hall

Page 1 of 3

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus