የጀርመን ፖሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡

Wednesday, 05 December 2018 09:09

የጀርመን ፖሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡ የጀርመን ፖሊስ ለኮሚሽኑ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተገልጾል፡፡

ህዳር 25ቀን 2011 ዓ.ም የጀርመን ፖሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት ዩርገን ሹበርት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡jer 1

በውይይቱ ላይ ሜጀር ጄነራል ደግፌ በዲ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በእድገቷ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከምትገኘው የጀርመን ሀገር ፖሊስ የሀገራችን የፖሊስ ተቋማት በርካታ መልካም ተሞክሮዎችን መቅሰም እንደለባቸው ተናግረው የሁለቱ ሀገራት ፖሊሶች የቀደመ ግንኙነት እንዳላቸው እና ጀርመን የኢትዮጵያን ፖሊስ ለማጠናከር ልዩ ልዩ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን በማስታዎስ አሁንም ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡  jer 2

የጀርመን ፌደራል ፖሊስ ምክትል ፕሬዚዳንት ዩርገን ሹበርት በበኩላቸው ኢትዮጵያ በለውጥ ጉዳና ላይ መሆኗን መረጃ እንደላቸው ገልፀው የሀገሪቷን የፖሊስ አቅም ለማጎልበት እና ተባብረው መስራት በሚያስችልበት ጉዳይ ዙሪያ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያን ፖሊስ አቅምን ለማጎልበት በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡jer 3

Rate this item
(1 Vote)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus