የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከጀስቲስ ፎር ኦል-ፒኤፍ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ስለጠና ሠጠ፡፡

Tuesday, 25 December 2018 11:56

አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከጀስቲስ ፎር ኦል-ፒኤፍ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብት ዙሪያ በአዳማ ከተማ ለኮሚሽኑ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስለጠና ሠጠ፡፡ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ

ታህሳስ 11 እስከ 13 ቀን 2011 ዓ.ም   በአዳማ ከተማ በተሰጠው ስልጠና ላይ ተገኝተው የስራ መመሪያ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እንደገለፁት በሀገራችንም ሆነ በተቋማችን የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ለመስቀጠል ማህበረስቡ በየደረጃው የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በፍጥነት ከመመለስ አንፃር ሳይንሳዊ በሆነ የአመራር ክህሎት በመታገዝ ሰዎች በተፈጥሮ ያገኙትን ሰብአዊ መብታቸውን በማንኛውም ሁኔታ እንዲከበር ለማድረግ ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው ለለውጡ መሳካት የአመራርንት ሚናቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ ኮሚሽኑ ከመቼውም ጊዜ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን ም/ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡km mekonen

የኮሚሽኑ ፖሊስ አካዳሚ ዳይሬክተር ረ/ኮሚሽነር መኮንን አሻግሬ በበኩላቸው የፖሊስ ተቋም አመራሮችና አባለት ሰብአዊ መብትን አክብሮ የማስከበር ድርብ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስታውሰው በተወሰ መልኩ በፀጥታ ኃይሉ የሚስተዋሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል ስልጠናው ለአመራሩ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር ስለታመበት መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡

የፖሊስ አመራር ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ በቅድሚያ ጥሰቶቹን አስቀድሞ መከላከል ይገባል፡፡ ጥሰቶች ተፈፅመው ሲገኙ በፍጥነት ለህግ በማቅረብ ረገድ ፖሊስ ህገ መንግስቱንና በስሩያሉትን ህጎች መሰረት አድርጎ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ መጠን ሰባአዊ መብቶችን አስቀድሞ ከማስከበር በተጨማሪ የማስከበር ግዴታውን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ስልጠናውን የሰጡት ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ ገልፀዋል ፡፡Docter  sisay

ለአመራሮቹ ስልታዊ የአመራር ዘዴዎች በተመለከተ እንደተቋም የለውጥ ግለቱን ለማስቀጠል አመራሩ ዘመኑ የሚጠይቀውን ሳይንሳዊ የአመራር ጥበብን በመጠቀም ቀልጣፋና ተደራሽ በየትኛውም ሁኔታ ለህግ የበላይነት ተገዥ የሆነ ቨመራር መኖር እንዳለበት ረ/ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ተሾመ ገልፀዋል፡፡hall

Last modified on Tuesday, 25 December 2018 12:07
Rate this item
(3 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus