በ9 ወር የተከናወኑ የፀጥታ ማስከበር ስራዎችን በጋራ ገምግመዋል

Monday, 22 April 2019 08:02

       የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም ፤ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና የሌሎች አስፈፃሚ አካላትን የ2011 በጀት ዓመት በ9 ወር የተከናወኑ የፀጥታማስከበርስራዎችን በጋራ ገምግመዋል፡፡በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡11

     በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሚያዚያ 10 ቀን 2011 ዓ.ም የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የተከበሩ አቶ ኤፍሬም ግዛው የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም ፡ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፤ እና ሌሎች የም/ቤቱ አባላት፤የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ፤ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፤የሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና ከደንብ ማስከበር ዘርፍ የተውጣጡ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡  22

  

     የአዲስ አበባ ፖሊሰ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በመዲናችን ወንጀልን እና የትራፊክ አደጋን   ለመቀነስ እንዲሁም የተጀመረውን ሃገራዊ ለውጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የኮሚሽኑ አባላትና አመራር ልዩ ትኩረት ሰጥተው ለህብረተሰቡ ስጋት የሆኑ ወንጀሎችን ለመቀነስእየሰሩ መሆኑን ገልፀው ፡ ከሪፖርቱ የተገኙ መልካም አፈፃፀሞችን በማጠናከርና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በቀጣይ ከከተማው ማህበረሰብ፤ከአስፈፀሚና ከአስተዳደር አካለትጋር በመቀናጀት እንደሚሰሩ በመጠቆም የህ/ቡ እና የተቋማት ድጋፍና አጋርነት ወሳኝ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡ 33 

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሰላም፤ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ኤፍሬም ግዛው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተማውን ሁለንተናዊ ሰላም በማስፈን በርካታ የሚታዩና የሚለኩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡በቀጣይ በጋራ በመተባበር የተጀመረውን ለውጥ እንዳይደናቀፍ ማስቀጠል፤የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት፤የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እና ሌሎች መልካም ተግባራት በተቀናጀ መልኩ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችም በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡      

በዕለቱ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የዕቅድና በጀት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ማሞ የአስፈፃሚ ተቋማት በጋራ ለመስራት ያቀዱትን የህዝብ ስራ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ እና ያለ ህዝብ ትስስር የሚሰራ ስራ ውጤቱ አርኪ ስለማይሆን ከምንም በላይ የህ/ቡ ተሳትፎ ማደግ አለበት ብለዋል፡፡44

Rate this item
(2 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus