ከፖሊስ የሙያ ስነ-ምግባር ውጪ በአንዲት ግለሰብ ላይ ድብደባ የፈፀሙ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ዉለዉ ምርመራ እየተጠራባቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

Monday, 04 October 2021 09:25
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ሚካኤል አደባባይ አካባቢ መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ም/ኢ/ር ጃፋር አሊ እና ኮንስታብል መስፍን በተለ የተባሉ የቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አባላት አንዲትን ግለሰብ በአስነዋሪ ሁኔታ በመደብደባቸው በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጠራ ይገኛል፡፡
ህዝብን በሰብአዊነት ማገልገል የአዲስ አበባ ፖሊስ መርህ መሆኑ እየታወቀ ነገር ግን አንዳንድ አመራሮችና አባላት ይህን መርህ በመተላለፍ የሚፈፅሙት ህገ-ወጥ ድርጊት ተቋሙ የማይታገስ መሆኑን ገልፆ በ2013 የበጀት ዓመት ብቻ እንኳን በልዩ ልዩ ጥፋት ላይ የተገኙ 171 የፖሊስ አመራሮችና አባላት ከሰራዊቱ እንዲሰናበቱ አድርጓል፡፡
ከስራ ከተሰናበቱት 29ኙ ከሰብአዊ መብት ጥስት ጋር በተያያዘ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል። ህግን በመተላለፍ ጥፋት በሚፈፁም አባላት እና አመራሮች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፖሊስ አስታውቆ ህብረተሰቡ እንዲህ ዓይነት ከፓሊስ የሙያ ስነ- ምግባር ውጪ የሆኑ ድርጊቶች በሚፈፀሙበት ወቅት በፍጥነት ጥቆማ እንዲያደርግ እየገለፅን ግለሰቧን በደበደቡ የፖሊስ አባላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዶ ውጤቱን ለህዝብ የሚሳውቅ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡
Last modified on Monday, 04 October 2021 09:32
Rate this item
(2 votes)

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus