የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦክስ ፌዴሬሽን ከጎጆ ክሬቲቭ ሚዲያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የስፖንሰር የቦክስ ውድድር ላይ የተስተዋለው ስፖርታዊ ጨዋነት ለሌሎች አርአያ እንደሆነ ተገለፀ፡፡
ሪፖርተር፡- ኮን/ል አባበል ከበደ

rsz ai4a1051ጥቅምት 19 ቀን 2010 ዓ/ም አ/አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ከጎጆ ክሬቲቪ ሚዲያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ውድድር ላይ ከልዩ ልዩ የስፖርት ክለቦች የተወጣጡ የቦክስ ስፖርተኞች ተሳትፈውበታል፡፡
በዕለቱ ውድድሩን ለመከታተል በርካታ ቁጥር ያለው የስፖርት አፍቃሪ የታደመ ሲሆን ውድድሩ ስፖርታዊ ጨዋነት በተላበሰ መልኩ መጠናቀቁ የሌሎች ስፖርታዊ ውድድሮች ምሳሌ እንደሆነ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንት አቶ አብዱ ሰመር መሀመድ እና የአ/አ/ከተማ ቦክስ ፌዴሬሽን ም/ሃላፊ አቶ አሰፋ አብርሀ ገልፀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ስፖርት ማስተባበሪያ ሀላፊ ም/ኢ/ር ያረጋል ሙሉ በበኩላቸው ውድድሩ በጥሩ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የሚመለከታቸው አካላት ድርሻቸው እንደተወጡ ተናግረዋል፡፡ በተለይ ስፖርት አፍቃሪው ለስፖርቱ ማደግ እያደረገ ያለው ቀና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡
በውድድሩ ላይ በ49 ኪ.ግ የአዲስ አበባ ፖሊሱ እንዳሻው አላዩ ከኢ/ያ ወጣቶች አካዳሚ ዳዊት ፍቃዱን፤ በ64 ኪ.ግ የአዲስ አበባ ፖሊሱ መስፍን ብሩ የማራቶን ክለቡን ተመስገን ምትኩን በማሸነፍ የወርቅ ሚዳሊያ ያጠለቁ ሲሆን በ75 ኪ.ግ ሁለቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ቦክሰኞች መክብብ ከማል እና ሰይፈ ከበደ የተገናኙ ሲሆን ሰይፈ ከበደ አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡rsz ai4a1031rsz ai4a1067

 

rsz ddለህክምና የመጣችውን የ3 ልጆች እናት አስገድዶ የደፈረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር

አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ ገለፀ፡፡
ሪፖርተር፡- ዋ/ሳጅን ከድር መሀመድ

ነሀሴ 10 ቀን 2009 ዓ/ም ነው ወንጀሉ የተፈፀመው፡፡ ቦታው ደግሞ በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ካለው አንድ የጤና ተቋም ውስጥ ነው፡፡
ተጠርጣሪው ተቀጥሮ ከሚሰራበት የጤና ተቋም ለህክምና የመጣችውን የ3 ልጆች እናት የጤና ምርመራ ካደረገ በኋላ የህክምናዋን ውጤት እንደምትወስድ ይቀጥራታል በቀጠሮ ቀን የተገኘችው ታካሚ የህክምናዋን ውጤት ልስጥሽ በሚል ምክንያት ቢሮ እንድትገባ ካደረገ በኋላ ድርጊቱን መፈፀሙን የጉዳዩ መርማሪ ዋ/ሳጅን አውራርስ እሱባለው ተናግረዋል፡፡
በማስረጃ የተደገፈውን የምርመራ መዝገብ ዋቢ ያደረጉት መርማሪው ይህን መሰል ህክምና ስነ-ምግባር ድርጊት ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

 

ሪፖርተር፡- ዋና ሳጅን ከድር መሀመድ

images 4 

 

 

መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ/ም ነው ወንጀሉ የተፈጸመው ቦታው ደግሞ በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ማርያም ቤ/ክ ቅጥር ግቢ ነው ፡፡

 

ተከሳሽ ወደ ቤተክርሰቲያኑ ቅጥር ግቢ በመግባት ከተቀመጠው ሙዳይ ምፅዋት ሳጥን የመርፌ ቁልፍ በመጠቀም 2 መቶ ብር ሲያወጣ በቦታው የነበሩ ምዕመናን ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር እንደዋለ የባልቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ተወካይ የሆኑት ኢ/ር መስፍን ምትኩ ተናግረዋል፡፡

 

እንደ ሀላፊው ገለፃ ተከሳሽ በተለያየ ጊዜያት በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት በመግባት ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት እንደሚፈፅም የምርመራ መዛግብቱንና የኋላ ታርኩን ዋቢ በማድረግ ገልፀዋል፡፡ የተከሳሽን ምርመራ መዝገብን ተጠናቆ ለውሳኔ ለዐቃቤ ህግ መቅረቡንም ተናግረዋል፡፡

 

በቤተክርስቲያናት ውስጥ ለአምልኮ የሚመጡ ምዕመናንን ተመሳስሎ የወንጀል ድርጊት የሚፈፅሙ ግለሰቦች ሊኖሩ ስለምችሉ አብያተ ክርስቲያናቱ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርጉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ 

 

22449990 1932790426969537 9116884659905608118 n‹‹ ራዕይ ሠንቀናል ለላቀ ድል ተነሳስተናል!! ››
‹‹ ራዕይ ሠንቀናል ለላቀ ድል ተነሳስተናል!! ››

በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 10ኛዉ ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀንን ለማክበር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከ3መቶ በላይ በየደረጃዉ ከሚገኙ የፖሊስ አመራሮች ጋር ጥቅምት 2 ቀን 2010 ዓ.ም በኮሚሽኑ ሠላም አዳራሽ ዉይይት አደረገ፡፡
በውይይቱ ላይ ስለ በዓሉ አከባበር እንዲሁም ስለ አዲሲቷ ኢትዮጵያ ታሪክ በዋናነት ተነስቶ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ተወያዮቹም ለሠንደቀ ዓላማ ክብር ሁሌም በፅናት እንቆማለን ሲሉ አሰተያየታቸዉን ሰጥተዋል፡፡22365280 1932791820302731 379425205202232718 n

policenews

በአ/አበባ ከተማ በተለያዩ ክ/ከተሞች ጊዜ ተወስዶ በተደረገ ሰፊ ጥናት ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች በ88 የተለያዩ የወንጀል ፈፃሚዎች ቡድን የተደራጁ 216 ግለሰቦች መሆናቸውን የገለፁት በኮሚሽኑ የኢኮኖሚና የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዲቪዚዮን ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር አበራ ቡሊና ናቸው፡፡

ሐምሌ 30 ቀን 2009 ዓ/ም በቢሯቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳብራሩት ጊዜ በወሰደው ጥናት ከቅሚያ ወንጀል ጀምሮ በርካታ ቁጥር ያለው የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችና የኢትዮጵያ ብር እንዲሁም የተለያየ ደረጃ ያላቸው አደንዛዥ እፆች ከግለሰቦቹ ጋር ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ጨምረው ገልፀዋል፡፡


ለስራው ውጤታማነት ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠትና ጥቆማ በማድረግ ያደረገው ትብብር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው የገለፁት ኃላፊው ፖሊስ የምርመራ መዝገብ አደራጅቶ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ለማቅረብ በዝግጅት ላይ ነው ብለዋል፡፡

መሰል የወንጀል ድርጊቶች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትሉት ተፅእኖ ከፍተኛ በመሆኑ ፖሊስ ቀጣይነት ያለው ሰፊ ጥናቶችን በማድረግ ወንጀል ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ገልፀው የህብረተሰቡ ትብብር በቀጣይነትም ለፖሊስ ስራ ወሳኝ በመሆኑ ትብብሩ እንዲቀጥል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡  

በኦሮሚያ ክልል ሰበታ ሃዋስ ወረዳ ላይ በሚገኘው የደብል ተራራ ላይ የኮሚሸኑ አመራርና አባላት የችግኝ ተከላ ያካሄዱት ሐምሌ 23 ቀን 2009 ዓ.ም ነው፡፡ በዕለቱ ‹‹ ለአረንጓዴ ልማታችን ስኬታማነት ሁሌም በትጋት እንሰራለን ›› በሚል መሪ ቃል በተደረገው የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአ/አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ተስፋዬ ደንደና እንደገለፁት ከ2005 ዓ.ም በፊት የተራቆተውን የደበል ተራራ መልሶ ለማልማት የኮሚሽኑ አመራርና አባላት ለተከታታይ 4 አመታት ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ስፍራው ከመልማቱ በጠጨማሪ ለአካባቢ ወጣቶች ኮሚሽኑ የለገሳቸው የንብ ቀፎ በምን ደረጃ እንዳ በጤና ጥበቃ ሚንስተር ዴታና መ/ኮሚሽነር ተስፋዩ ደንደና ተጎብኝቷል፡፡ በችግኝ ተከላው ፕሮግራም ላይ የተገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት ከ45 ሺ ችግኞች በላይ መትከላቸውን በዕለቱ ተገልጿል፡፡ 

newsplantation

 

የአ/አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተማውን ሰላምና ፀጥታ ከማስጠበቁ በተጨማሪ በአካባቢያቸው እያደረገ ያለው የአረንጓዴ ልማት ስራውን የበለጠ ሊያጠናክር ይገባል ሲሉ የሃዋስ ወረዳ ነዋሪዎች ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል፡፡ 

 

 

ሃይሉ ቡናሮ ወንጀሉን የፈፀመው ግንቦት 27 ቀን 2009 ዓ/ም በአራዳ ክ/ከተማ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የአ/አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት መነሻ ፌርማታ አካባቢ ነው፡፡

ንብረት

ተከሳሹ በተጠቀሰው ቀን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በመግባት ግምታቸው 6 ሺ 3 መቶ ብር በላይ የሚያወጡ 4 የእሳት ማጥፊያዎችን ከሰረቀ በኋላ እስክ ነጋ ባቡር በመጠበቅ ላይ እያለ እንቅልፍ ወስዶት ከነንብረቱ መያዙን የፌ/ጠ/ዐ/ህግ አቶ አብርሃም አያሌው ገልፀዋል፡፡

በተከሳሹ ላይ የተደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት በነሀሴ 27 ቀን 2009 ዓ/ም ውለው ሃይሉ ቡናሮን ጥፋተኛ በማለት በ1 አመት ከ8 ወር እስራት እንድቀጣ የወሰነበት መሆኑን የምርመራው መዝገብ ያስረዳል፡፡

መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለወንጀል መፈፀም ምቹ የሆኑ ንብረቶቻቸውን በተገቢ ሁኔታ እንድጠበቁ በማድረግ ወንጀልን አስቀድመው ሊከላከሉ እንደሚገባ ሃላፊው ገልፀዋል፡፡

ወንጀሉ የተፈፀመው የካቲት 14 ቀን 2009 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ሲሆን በን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ልዩ ቦታው ላፍቶ ባንኮች ማህበር እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ሟች አቶ ተወልደ ገ/አምላክ በመኖሪያ ቤታቸው መኝታ ክፍላቸው ውስጥ ተኝተው እያለ እንዲሁም የቤት ሰራተኛቸው ሟች ትህትና ውብሸት የተባለችው ደግሞ በሌላኛዋ መኝታ ክፍል ውስጥ ተኝተዋል፡፡

የሟች ዘመድ የሆነው ተከሳሽ በቅርቡ በሟች ቤት በእንግድነት መጥቶ ከአቶ ተወልደ ጋር እየኖረ ነበር፡፡ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ቤቱ ውስጥ ያሉትን ንብረቶች ካጠና በኋላ የመኖሪያ ቤቱን የበር ቁልፍ በእጁ በማድረግ ቤቱን ለመዝረፍ ከሌሎች ግብረ አበሮች ጋር በመስማማት ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ሟች አቶ ተወልደ ከመኝታቸው የቅርብ ዘመዳቸው ተጠርጣሪ የሻወር ቤቱ ውሃ እየፈሰሰ ነው በሚል ምክንያት ከጠራቸው በኋላ በገጀራ በመምታት ህይወታቸው እንዲያልፍ ካደረጉ በኋላ በሌላኛው መኝታ ክፍል የተኛችውን ሟች ትህትና ውብሸትን ከተኛችበት ቀስቅሰው የተፈፀመውን ድርጊት አይታለች ለፖሊስ ትናገራለች በሚል ሰበብ በተመሳሳይ ሁኔታ እሷንም ከገደሏት በኋላ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ ያገኙትን ጥሬ ገንዘብ ላፕቶፕ ሁለት ታፕለት ሞባይሎችና ካሜራ እንዲሁም የሟች አልባሳትና ጫማ በመውሰድ የመኖሪያ ቤቱን በር ዘግተው ይሰወራሉ፡፡

ሟች አቶ ተወልደን ለ2 ቀናት በአካባቢው ያጡ ጎሮቤቶች ተጠራጥረው ለዘመዶቻቸው በመደወል እንደሌሉ በመግለፃቸው ቁልፍ በማስመጣትና ለፖሊስ በመደወል የካቲት 16 ቀን 2009 ዓ/ም የመኖሪያ ቤቱ በር ሲከፈት ሞተው በመገኘታቸው ምርመራው እንደተጀመረ የነገሩን የአ/አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሰው መግደል ምርመራ ክፍል መርማሪ ዋና ሳጅን መንግስቱ ታደሰ ናቸው፡፡

ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ቆይታ ያደረጉት ዋና ሳጅን እንደገለፁት ወንጀሉን ማንይፈፅማል የሚለውን የክትትል ቡድኑና የምርመራ ክፍሉ በመ ቀናጀት ባደረጉት ጥረት 2ቱን ወንጀል ፈፃሚዎች በመያዝና በመመርመር ወንጀሉን እንደፈፀሙ በማመን ኢግዚቢቶች እንደተያዘባቸው ተናግረዋል፡፡

እንደ መርማሪው ገለፃ በተያዙት ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላካቸውን ገልፀው ያልተ ያዙትን ተጠርጣሪዎች እና ንብረት ለማስመለስ ጥረት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የሟች አቶ ተወልደ ቤተሰቦችን አግኝተን ባነጋገርንበት ወቅት ወንጀል ፈፃሚዎቹ ይያዛሉ ብለው እንዳላሰቡ ገልፀው በአጭር ጊዜ ውስጥ ማንነታቸው ታውቆ በመያዛቸው እንደተሰቱ ተናግረዋል፡፡  

Page 3 of 3

የቪድዮ ክምችት

ቪድዮዎች

በብዛት የታየ ቪድዮ

አሽከርክር ረጋ ብለህ

ፎቶዎች

Social Media

fbtwitteryoutubegoogleplus